አንድ አይበቃህም ተመለስ ራስህን ማወቅ ተስኖሃል ዛፉን ከሰዎች መለየት እንዴት ይቻልሃል? የእውቀት ዓይንህ ሲበራ መዳሰስ ልመድ አንዳንዴ ተቀመጥ ከአባቶችህ እግር ብቃት አይገኝም በአንዴ ድጋሜ ተዳሰስ መጥተህ አይኖችህ አጥርተው ይዩ ተለማኝ ከለማኝ ዛፉን ከሰው እንዲለዩ (ወርቅነሽ ቱፋ)
የእኔ ነገር
ጴጥሮስን አማለው ጌታን ካደ ብዬ ከኃጢአት እሳት ዳር ከዓለም ጋር ቁጭ ብዬ ይሁዳ ነህ አልኩት አቅልዬ ወንድሜን ስንት ጊዜ ሽጬው ለውጬው ጌታዬን ሰጡት ብዬ አዝናለው ሰፍነግና ሃሞት ስግተው እየኖርኩ የኃጢአቴን ገፈት የዘመኑ ዴማስ እያልኩ እተቻለው ከነዓን ሳልገባ መንገድ ላይ እያለው እንዲህ ነኝ ስጠቁም ጣቴን ወደሌላ ለራሴ አበጅቼ የኃጢአት ከለላ & ...
ኃጢአተኛ ከሆንክ በቅድስናው ደጅ ምን ትሠራለህ?
ብዙውን ጊዜ ወጣት ወንዶችና ሴቶች እንዲሁም ከብዙዎች ስሜት መረዳት እንደሚቻለው በኃጢአት ስንወድቅና በኛ ውስጥ ያለው ክርስቲያናዊ ማንነት ከሰዎች ሁሉ በተለየ መልኩ ቆሻሻ ሆኖና መስሎ ከታየን፤ ከቅድስት ቤተክርቲያን፤ ከጸጋው ግምጃ ቤት፤ ከምሕረቱ አደባባይ መራቅን እንደ መፍትሔ አድርገን እንወስዳለን፡፡ ምክንያቱስ ያልን እንደሆነ ጥንተ ጠላትዲያቢሎስ ሰዎችን የግሉ የሚያደርግበት ትልቁ ታክቲክ ቢኖር፤ ...
ልደታ ለማርያም
እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የልደት በዓል አደረሰን!!! ንጽሕተ ንጹሐን፣ ቅድስተ ቅዱሳን፣ ከተለዩ የተለየች፣ ከተመረጡ የተመረጠች ክብርት እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በከበረች ቀን ግንቦት አንድ ቀን ተወለደች፡፡ የመወለዷም ነገር እንዲህ ነው፡፡ በጥሪቃና ቴክታ የተባሉ የእግዚአብሔር ሰዎች ነበሩ፤ ባለጸጎች ቢሆንም ልጅ ግን አልነበራቸውም፡፡ ከዕለታት አንድ ቀን ቴክታ ሕልም ...
ትሕትና ምንድር ነው?
ትሕትና ምንድር ነው? ብዙ ጊዜ በእኛ ዘንድ የተናቀ ልብስ መልበስ ፣ አንገት መስበር ፣ ዝግ ብሎ ማውራት እና ‹እኔ በደለኛ የማይገባ ሰው ነኝ› እያሉ ደጋግሞ መናገር እንደ ትሑት ያስቆጥር ይሆናል፡፡ ነገር ግን የትሕትና ትርጉም ከዚህም በላይ ነው፡፡ በርግጥ ከላይ የዘረዘርናቸው ነገሮች የአንድ ትሑት ሰው ከፊል መገለጫ ጠባያት ተደርገው ሊወሰዱ ይችላሉ፡፡ ይሁን እንጂ እነዚህን በማድረግ ብቻ ትሑት መ ...
በዓለ ፅንሰት
በዓለ ፅንሰት ዛሬ መጋቢት ፳፱ ዓለም የተፈጠረበት፣ ጌታ የተፀነሰበት፣ ሞትን ድል አድርጎ የተነሣበት፣ ይህ ዓለም የሚያልፍበት ዛሬ ያ ነቢዩ ዳንኤልን ደም ግባቱ እስኪሽ ያስሰገደው መልአክ እየሰገደ በታላቅ ትሕትና የመጣበት ነው። ካህኑ ዘካርያስን ከግርማው የተነሣ ያስደነገጠው መልአክ እየፈራ እየተባ እመቤታችንን ያበሠረበት ነው። ደነገጠች የሚል ቃል የተጻፈው መደነቋን ለማጠየቅ እንደኾነ ...
ንጉሥ በአህያ ላይ
(ሽራፊ ሃሳብ ከሆሳዕና ምንባብ) "አህያ" ስምዋ ስድብ ከሆነ የቆየች እንስሳ ናት። የዚህች በዓለም ሁሉ የምትገኝ እንስሳ የሕይወት ታሪክዋ በአብዛኛው ተመሳሳይ ነው። በሚበዙት ሀገራት አህያ ከባድ ሸክም ስትሸከም ትውላለች ፣ ደክሟት ለማረፍ ብትፈልግና ሸብረክ ብትል እንኳን በዱላ የሚመታት እንጂ "እስቲ አረፍ በይ" የሚላት የለም። ጀርባዋ በሸክም ብዛት የቆሰለ ፣ እግርዋ በጭነት ብዛት የተብረከረ ...
ስለ እኛ የታመመውን ምን አንደበት ይናገረዋል?!
እጅግ ጥልቅ የጸሎት ሕይወት የነበረው፣ አካሉ አልቆ በአጥንቶቹ እስኪቆም ድረስ የሚጾመው ተሐራሚው ቅዱስ አባ ጳጉሚስ ከእለታት በአንዱ ቀን ይህን ተመለከተ፡፡ ቅዱሱ ዓርብ ዓርብ የጌታችንን ሕማማት እያሰበ ከእንባ ጋር አብዝቶ ይሰግድ ነበር፡፡ ከዓይኑ የሚወርደው እንባ ከሰውነቱ ወዝ ጋር እየተቀላቀለ ወደ መሬት በመውረዱ ምክንያት የሚሰግድበትን ቦታ አረጠበው፡፡ አባ ጳኩሚስም ይህን ወደ ጌታው እያመለከተ ...
የ ዕለተ መጻጉዕ ጉዞ
ዕለተ መጻጉዕን ምክንያት በማድረግ በተደረገው በትለንተናው የጉዞ መርሐ ግብር ልደታ ጸበል አካባቢ ወደሚገኘው የታዳጊዎች ማረሚያ ቤት በመሄድ ታራሚዎችን አጽናንተን ትልቅ በረከት ይዘን ተመልሰናል።










